ላይኮስ ተኢው ስው እር አንልግኤት
()
About this ebook
ላይኮስ የሚለው የግሪክ ትርጉሙ ክህሎት የሌለው ማለት ነው፡፡ታሪክ በተደጋጋሚ 'ልዩ ክህሎት' ባልተጎናጸፉ ሰዎች ታላላቅ ሁነቶች እንደተከወኑ ያስተምረናል በትርፍ ጊዜያቸው የሚገለግሊ ሰዎች በቤተክርስቲያን ውስጥ የማይሰሩ ከሆነ፣ ሸክምን በትርፍ ጊዜያቸው ለሚያገለግሉ ሰዎች ማካፈል እና ለምን የትርፍ ጊዜ አገልግሎትን ለመጠበቅ መዋጋት እንዳለብን በዚህ የዳግ ሂዋርድ ሚልስ ዓይነተኛ መጽሐፍ አማካኝነት ተማር፡፡
Dag Heward-Mills
Bishop Dag Heward-Mills is a medical doctor by profession and the founder of the United Denominations Originating from the Lighthouse Group of Churches (UD-OLGC). The UD-OLGC comprises over three thousand churches pastored by seasoned ministers, groomed and trained in-house. Bishop Dag Heward-Mills oversees this charismatic group of denominations, which operates in over 90 different countries in Africa, Asia, Europe, the Caribbean, Australia, and North and South America. With a ministry spanning over thirty years, Dag Heward-Mills has authored several books with bestsellers including ‘The Art of Leadership’, ‘Loyalty and Disloyalty’, and ‘The Mega Church’. He is considered to be the largest publishing author in Africa, having had his books translated into over 52 languages with more than 40 million copies in print.
Related to ላይኮስ ተኢው ስው እር አንልግኤት
Related ebooks
የሚከሱህ ሰዎች Rating: 0 out of 5 stars0 ratingsመንፈሳዊ አደጋዎች Rating: 0 out of 5 stars0 ratingsሌሎች Rating: 0 out of 5 stars0 ratingsበዕብራውያን ላይ የተሰጡ ስብከቶች (I) - እምነታችሁን እንዴት ማጠንከር ትችላላችሁ? Rating: 0 out of 5 stars0 ratingsየጥንቱ ወንጌል ጥበብ (Amharic53) Rating: 0 out of 5 stars0 ratingsዝንጉዎቹ Rating: 5 out of 5 stars5/5አደገኞች ልጆች Rating: 0 out of 5 stars0 ratingsበሥዕል የተደገፈ የዕባዳዎች አፈጻጸም ፍቅህ Rating: 0 out of 5 stars0 ratingsውበት አውሬው እና መጋቢው Rating: 0 out of 5 stars0 ratingsበየቀኑ ከእግዚአብሔር ጋር ውጤታማ የጥሞና ጊዜ ሊኖርህ ይችላል Rating: 0 out of 5 stars0 ratingsንገራቸው Rating: 5 out of 5 stars5/5ዛፉ እና አገልግሎትህ Rating: 0 out of 5 stars0 ratingsልጄ ሆይ ትችያለሽ Rating: 0 out of 5 stars0 ratingsሰይመው! ይገባኛል በል!! ውሰደ!!! Rating: 5 out of 5 stars5/5ወደኋላ ማፈግፈግ Rating: 0 out of 5 stars0 ratingsበዘፍጥረት ላይ የተሰጡ ስብከቶች (VI) - የሰውን ዘር ከጥፋት የሚያድን የወንጌል ምስክር ሁኑ (Amharic 54) Rating: 0 out of 5 stars0 ratingsትልቅ ቤተክርስቲያን Rating: 2 out of 5 stars2/5አሥር የመጋቢምች ዋና ዋና ስህተቶች Rating: 0 out of 5 stars0 ratingsዳግም መወለድ ብሎም ገሃነምን ማስወገድ Rating: 0 out of 5 stars0 ratingsየመጋቢነት አገልግሎትህን ወደ ላቀ ደረጃ አሳድግ Rating: 5 out of 5 stars5/5ትእቢተኞች Rating: 0 out of 5 stars0 ratingsቤተ ክርስቲያን ትከል Rating: 0 out of 5 stars0 ratingsጣፋጭ የመንፈስ ቅዱስ ተፅዕኖዎች Rating: 4 out of 5 stars4/5በውኑ በውሃውና በመንፈሱ ዳግም ተወልዳችኋልን? Rating: 0 out of 5 stars0 ratingsይቅርታ ማድረግ አቀለለው Rating: 0 out of 5 stars0 ratingsእግዚአብሔርን ማገልገል ትልቅ ነገር ነው Rating: 4 out of 5 stars4/5መጐዳት፣ መሠዋት፣ መከራ መቀበል እና መሞት Rating: 5 out of 5 stars5/5መጽሐፍ ቅዱስህን አንብብ በየቀኑ ጸልይ Rating: 5 out of 5 stars5/5ትተውህ የሚሄዱ ሰዎች Rating: 2 out of 5 stars2/5አገልግሎትህን አጉላው በመንፈስ ቅዱስ በሚደረግ ተዓምራትና መገለጦች Rating: 0 out of 5 stars0 ratings
Reviews for ላይኮስ ተኢው ስው እር አንልግኤት
0 ratings0 reviews
Book preview
ላይኮስ ተኢው ስው እር አንልግኤት - Dag Heward-Mills
ስለ ትርፍ ጊዜ አገልገሎት ማወቅ የሚገባህ ሰባት ነገሮች
ካልተገለፀ በቀር፣ በዚህ መጽሐፍ ውስጥ ያሉ ጥቅሶች ሁሉ የተወሰዱት በ 1954 ዓ.ም. ከታተመው የአማርኛ መፅሐፍ ቅዱስ ነው፡፡
Find out more about Dag Heward-Mills at:
Healing Jesus Campaign
Write to: evangelist@daghewardmills.org
Website: www. daghewardmills.org
Facebook: Dag Heward-Mills
Twitter: @EvangelistDag
Write to:
Dag Heward-Mills
P.o.Box 114
Korle-Bu
Accra
Ghana
ላይትሃውስ ቻፕል ኢንተርናሽናል
ስልክ + 251912063821
መ.ሳ ቁጥር 15134
አዲስ አበባ
ኢትዮጵያ
ISBN: 9781613954386
ይህን መጽሐፍ በሙሉም ሆነ በከፊል ያለ አሳታሚው ፈቃድ ማባዛት የተከለከተለ ነው፡፡
Table of Contents
ምዕራፍ 1. ሌይኮስ - 'ተራው ሰው'
ምዕራፍ 2. የትርፍ ጊዜ እና የበጎ ፈቃድ አገልጋዮች ባይኖሩ ምን ይፈጠራል?
ምዕራፍ 3. እግዚአብሔር በትርፍ ጊዜ ሰዎች የሚሰራበት ሰባት ምክንያቶች
ምዕራፍ 4. ስለ ትርፍ ጊዜ አገልገሎት ማወቅ የሚገባህ ሰባት ነገሮች
ምዕራፍ 5. ለምን የትርፍ ጊዜ መጋቢ መሆን እንደሚገባህ
ምዕራፍ 6. የትርፍ ጊዜ አገልግሎትን በምን አይነት መልኩ እንዳገኘሁት
ምዕራፍ 7. ሸክምን እንዴት ለትርፍ ጊዜ አገልጋዮች ማካፈል እንደሚቻል
ምዕራፍ 8. ዓይነተኛ የትርፍ ጊዜ መጋቢ
ምዕራፍ 9. ተገቢ የሆነ የትርፍ ጊዜ መጋቢ ባህሪ ምን ይመስላል?
ምዕራፍ 10. ሁለት ሀሳብ የሆኑ የትርፍ ጊዜ መጋቢዎች
ምዕራፍ 11. የትርፍ ጊዜ አገልግሎት የአገልግሎት ልኬት መሆኑን መረዳት
ምዕራፍ 12. የትርፍ ጊዜ አገልግሎት የእገዛ አገልግሎት ዓይነት መሆን መረዳት
ምዕራፍ 13. የትርፍ ጊዜ አገልግሎት ጉድለቶችን መረዳት
ምዕራፍ 14. እግዚአብሔር የትርፍ አገልግሎት ለምን እንዲኖር እንደሚፈቅድ መረዳት
ምዕራፍ 15. ለትርፍ ጊዜ መጋቢነት የሚረዱ አራቱ አስፈላጊ ክህሎቶች
ምዕራፍ 16. የትርፍ ጊዜ መጋቢዎች ትግሎች
ምዕራፍ 17. እራሳቸውን በፍቃዳቸው በሚሰጡ የአገልግሎት ተምሳሌት መሆን
ምዕራፍ 18. ለምን የትርፍ ጊዜ አገልግሎትን ለመጠበቅ መዋጋት እንዳለብን
ምዕራፍ 1.
ሌይኮስ - 'ተራው ሰው'
ተራ ሰው (ሌይ ማን) የሚለው ቃል 'ላይኮስ ከሚለው የግሪክ ስረወ ቃል የተገኘ ነው፡፡ ይህም ማለት 'ልዩ ክህሎት የሌለው ያልታደለ' ማለት ነው፡፡ ታሪክ 'ልዩ ክህሎት' ባልተጎናጸፉ ሰዎች ታላላቅ ሁነቶች እንደተከወኑ ያስተምረናል፡፡ ተራ በሚባሉ ሰዎች አማካኝነት የታዩ ከፍተኛ ውጤቶች ላይ የወፍ በረር ቅኝት እንኳ ቢደረግ እነዚህን አይነት ሰዎች በአገልግሎት ውስጥ ለመጠቀም መነሳሳትን ታገኛለህ፡፡ በተራ ሰዎች ብዙዎች ወደ ደህንነት መጥተዋል፤ በርካታ የቤት ህብረቶች ተመስርተዋል፤ አብያተ ክርስቲያናት አድገዋል፤ የእግዚአብሔርም ስራ ሰፍቷል፡፡
የሚከተሉት ተራ ሰው (ሌይማን) ለሚለው ቃል የተሰጡ ቀራቢ ትርጉሞች ናቸው
1. ሌይ ማን (ተራ ሰው) የተለመደ አይነት ሰው ነው
2. ሌይ ማን (ተራ ሰው) መደዴ የሚባል አይነት ሰው ነው
3. ሌይ ማን (ተራ ሰው) ተደጋጋሚ አይነት ፊት ያለው ሰው ነው
4. ሌይ ማን (ተራ ሰው) ልማዳዊ አይነት ሰው ነው
5. ሌይ ማን (ተራ ሰው) መደበኛ አይነት ሰው ነው
6. ሌይ ማን (ተራ ሰው) ልዩነት የማይታይበት ሰው ነው
7. ሌይ ማን (ተራ ሰው) የአዘቦት ሰው ነው
8. ሌይ ማን (ተራ ሰው) 'ምንም አይልም የሚባል' ሰው ነው
9. ሌይ ማን (ተራ ሰው) 'ባለሙያ ያልሆነ ሰው ነው
10. ሌይ ማን (ተራ ሰው) ሊቅ ያልሆነ ሰው ነው
11. ሌይ ማን (ተራ ሰው) ያልተጠበበ ሰው የሚባል ነው
12. ሌይ ማን (ተራ ሰው) ልዩ ክህሎት የሌለው ሰው ነው
13. ሌይ ማን (ተራ ሰው) ያልሰለጠነ ሰው ነው
14. ሌይ ማን (ተራ ሰው) የምስክር ወረቀት የሌለው ሰው ነው
ሌይ ማን (ተራ ሰው) የሙያ ፈቃድ ማረጋገጫ ወረቀት የሌለው ሰው ነው
በቤተክርስቲያን ድባብ ውስጥ የተደረጉ ታላላቅ ክንውኖች
1. ተራ ሰዎች የታላቁ የቤተክርስቲያን ተሐድሶ አምዶች ናቸው
ማርቲን ሉተር መጽሐፍ ቅዱስን ወደ ተራው ሰው ቋንቋ መተርጎሙ የዓለምን መልክ ለመቀየር አስችሎታል፡፡ በላቲን ቋንቋ የተጻፈውን የእግዚአብሔር ቃል በአፍ መፍቻ ቋንቋ ለህዝቡ እንዲደርስ አደረገ፡፡ እናም የመገለጥ እውቀት አንድ ጊዜ በተራ ሰዎች መዳፍ ስር ሲገባ አለምን መለወጥ ቻሉ፡፡ በዚህም ሰዎች ሁሉ ደህንነትን በእግዚአብሔር ጸጋ መውረስ እንደሚችሉ ሲገነዘቡ በብርታት እና በሐይል ከፍ ብለው በአሸናፊነት በመነሳት ተሐድሶ የምንለውን አስገኙ፡፡
2. ተራ ሰዎች ለታላቋ የሜቶዲስት ቤተክርስቲያን አምዶች ነበሩ
በ20ኛው ክፍለ ዘመን አጋማሽ ሜቶዲዝም በዩናይትድ ስቴትስ አሜሪካ ውስጥ ትልቋ የፕሮቴስታንት ቤተእምነት ነበረች፡፡ ይህች ታላቅ ቤተክርስቲያን ታዲያ በብርታት መገስገስ የቻለችው በተራ ሰዎች ጫንቃ አማካኝነት ነበር፡፡ ጥንታዊው የሜቶዲስት ቤተክርስቲያን ልማድ 'ኡደት' በተባለ የሜቶዲስት ስብስብ ቤተክርስቲያናት ውስጥ የትርፍ ጊዜ ሰባኪን የአምልኮን አገልግሎት እንዲመራ ብሎም ቃሉን እንዲሰብክ መሾም ልማድ ነበር፡፡
የትርፍ ጊዜ ሰባኪውም በእግሩ ወይም በፈረስ አማካኝነት የተሰጠው የስብከት ጣቢያ (ኡደት) በመጓዝ በተለመደው ስርዓትና ጊዜ ያከናውናል፡፡
በዚህች ቤተ እምነት ከአገልጋዮችና መጋቢዎች መሾም በኋላም ይህ የትርፍ ጊዜ የስብከት አገልግሎት ልማድ 'የሜቶዲስት አገር በቀል ሰባኪያን' ተብለው የቀጠሉ ሲሆን በየአጥቢያ ቤተክርስቲያናቱ ይሾሙ ነበር፡፡ በምላሹም በየአቅራቢያው ባሉ ቤተክርስቲያናት ይጋበዙና ይሾሙ የነበር ሲሆን የአገልጋዩ ረዳት ወይም ደግሞ በተለየ አቅድ አገልጋዮች በሚቀሩበት ጊዜ አገልግሎቱን ባግባብ ይሸፍኑ ነበር፡፡
3. ተራ ሰዎች በዓለም ላይ በተናጠል ትልቅ ለሆነችው ቤተክርስቲያን አምድ ነበሩ፡፡
የዮይዶ ፉል ጎስፕል ቤተክርስቲያን ከተመሰረተችበት መሰረታዊ መርሖች አንዱ በትርፍ ጊዜ አገልጋዮች አማካኝነት አገልግሎት መስጠት የሚል ነው፡፡
የዮይዶ ፉል ጎስፕል ቤተክርስቲያን በዴቪድ ያንግ ቾ እና በአማቱ ቾይ ጃሺል አማካኝነት የተመሰረተ ሲሆን ሁለቱም ቀድሞ የአሴምብሊስ ኦፍ ጋድ መጋቢያን ነበሩ፡፡ የመጀመሪያውን የአምልኮ አገልግሎት ሜይ 15/1958 በቁጥር አራት ከሚሆኑ ልጃገረዶች ጋር በቾይ ጃ ሺል መኖሪያ ቤት አደረጉ፡፡ በ1977 የቤተክርስቲያናቱ አባላት ሐምሳ ሺህ ከደረሱ በኋላ በሁለት አመት ውስጥ እጥፍ ሆኑ፡፡ በኖቬምበር 30/1981 አባላቱ 200,000 የደረሱ ሲሆን በዚያኑ ጊዜ ሎሳንጀለስ ታይምስ የተባለው ጋዜጣ በዓለም ትልቁ አጥቢያ ቤተክርስቲያን በማለት አትቷል፡፡
በ2007 የአባላቱ ቁጥር 830,000 የደረሰ ሲሆን የእሁዱ የአምልኮው መርሐ ግብር በ7 ፈረቃ ፣በ16 ቋንቋዎች እየተተረጎመ ይካሔዳል፡፡
4. ተራ ሰዎች በጋና እና ናይጄሪያ ከተነሱት ግዙፍ የቤተክርስቲያናት መረብ አምዶች ናቸው፡፡
መቀመጫውን በናይጄሪያ ያደረገው የሪዲምድ ክርስቲያን ቸርች ኦፍ ጋድም ሆነ መናገሻውን ጋና ያደረገው ቸርች ኦፍ ፔንቴኮስት ሁለቱም ተራ ሰዎችን በአገልግሎት ውስጥ በሚገባ በማሰማራት ይታወቃሉ፡፡ እነዚህ ሁለቱም አግልግሎቶች ግዙፍ የሆነ የመያያዝ መረብ የፈጠሩ ሲሆን በመደበኛነት የትርፍ ጊዜ አገልግሎት ማለትም የወንጌል ስብከትም ሆነ የመጋቢነት አገልግሎት ይሰጣል፡፡
የጴንጤቆስጤ ቤተክርስቲያን የተመሰረተችው ከእንግሊዝ ብራድፎርድ ከአፖስቶሊክ ቸርች ወደ ጎልድኮሰት (የአሁኗ ጋና) በተላከው አየርላንዳዊ ሚስዮናዊ ጄምስ ማኪዮን አማካኝነት ነው፡፡ ይህች ቤተክርስቲያን ከ 1.7 ሚሊዮን አባላት በላይ እስኪኖራት አድጋለች፡፡ የፔንቴኮስት ቤተክርስቲያን በአለም ላይ በ70 አገራት ውስጥ 13,000 አጥቢያ ቤተክርስቲያናት