Beruflich Dokumente
Kultur Dokumente
አዘጋጆቹ
የኔማ ጌታ የሰጠኝ ስንዴ
ገና ሳልበላዉ አበጠ ክንዴ
ወይ የኔ ጌታ የሰጠኝ ሙክት
እግንባሩ ላይ አለዉ ምልክት
መስከረም ጠባ እሱን ሳነክት
*ይህ በእንዲህ እንዳለበዚህ እትም ፅሁፋችሁ ያልተካተተ ወዳጆቻችንን በጣም ተንዛዝቶ አንባቢ እንዳያሰለች
ለሚቀጥለው እትም አቆይተነው እንጂ ችላ ብለን አይደለም እያልን ይቅርታችሁን እንለምናለን *
መልካም ንባብ
ተካኢ ሃይሌ
ኪሩቤል አጥናፉ
Telegram | https://t.me/aterira
Facebook | https://www.facebook.com/aterira
Call | +251 925 749 956
እትም-14 ነሐሴ| 2012
3
FIGHT OR FLIGHT
SELMAN HUSSEIN
I’m one of those people who “discovered” Tweeter during this Pandemic. I
don’t really have much interaction but, even as a “follower”, it’s a fascinat-
ing place. A place where accounts are verified, ideas go viral much more
easily and words count. And if you are a football fan, it’s all more interest-
ing. But enough beating around the bush and let’s cut to the chase.
Reading these threads, I couldn’t help but dwell between two sensations.
One, of course, was a mix of melancholy and empathy. I imagined the hor-
rors a young girl had to endure making her way in this brutal world. There
really is no room for justification. This is truly depressing. And savage. It
must STOP. Enough is enough!
I couldn’t stick to either sensation for long. As with most extreme argu-
ments, I thought there could be a benign middle where these opposing
lines of thought converge, somehow. I needed to borrow some skills from
Sherlock Holmes to reach that sweet spot. Or so it appeared.
Perhaps, that naughty voice at the back of my head was just guilty con-
science trying to avoid pointing fingers. I may have sexually harassed a girl
at some point in time or another, even in the mildest sense of the term,
and this is me avoiding confrontation. After all, what kind of a monster
blames a rape victim? Would I still argue if the assaulted was someone
close to me?
Therefore...
Ladies, I’m sorry you have to go through all this horror. I’m sorry for the
part I play in it. Say No to sexual harassment, and rightfully so. But don’t
just stop there. Focus on practical solutions. Don’t wait for empathy from
someone who will harass you the next day. This is a broken world. Learn to
defend yourself. Teach your daughters as well. Sue the bastard! Or call him
out. And, of course, the law should be strict enough to provide protection.
And boys, whenever you wine about a girl leaving you without a warn-
ing, try to imagine the kind of shit she lives through; the catcalling on the
streets, those predatory looks in every corner and the unsettling status
quo that conditioned her into a constant fight or flight mode. Perhaps the
እትም-14 ነሐሴ| 2012
6
part you had to play in your sudden break up was insignificant compared
to the baggage she is carrying. Perhaps it’s not entirely your fault. Perhaps
you were just a trigger.
-ምን
- ኧ...ረ ?
ከዛ በፊት አንድ ሁለቴ የዴክ ካሴት አልቆ ሳጠነጥን ጉዳዩን (ተውኔተ ወሲብ ) አይቻለሁ
። መጀመሪያ አንደመደንገጥ አርጎኝ ነበር ፥ ምን ጉድ ነው ? አይነት ። ድንጋጤው ሲበርድ
ተደብቆ የጉዱን ጉድ ማየት ጀመርኩ ። የተደበቀን የመሻት ጉጉት ይሁን ተፈጥሯዊ
የጉርምስና ሽፍደት እርግጠኛ አልነበርኩም ።
በፊልሙ ላይ አንዲት የመረብ ታይት ያደረገች የቢሮ ፀሐፊ ለአለቃዋ የነበራትን ፍቅር
በየአቅጣጫው በመተተጣጠፍ ስትገልፅለት ያሳያል ። ከዛን ግዜ አንስቶ አለቆችና ፀሐፊ
የተለየ ግኑኝነት ሊኖራቸውም እንደሚችል መገመት ጀመርኩ ። አሁን እንዲህ የተባ
እውቀት ከወዴት ይገኛል ?
ክፍሉ ውስጥ የነበረው ጫጫታና ወከባ ምቾት ሰጥቶናል ። እሙ መሀል ገብታ አንድ
በአንድ እየገለጠች አስኮመኮመችን ። ለአራት እንዳቀቀረቅረን አረ በስማምዬ! እያልን
ጉዳዩን አየን ።
(ስለፊልሙ ደሞ እንቀደድ)
የዛን አይነቱ አጋጣሚ በቀላሉ የሚገኝ አልነበረም። ያለኝ ምርጫ ያየሁትን እራሱን ደግሞ
መከራየት ነበር ። ለጓደኞቼ ሁሉ እየጠራሁ በምስጢር አሳየኋቸው ፥ ከአንዱ ጓደኛችን
በቀር *የባለጌ ነገሩን የጠላ አልነበረም ። እንደውም ብዙ ምርቃት አተረፍኩ ።
ምክትል ዳይሬክተራችን - ሃሃ
ታዲያ አንድ ሰውዬ ይመጣና ሚስቱ በሁለት አመት ሶስት ልጅ ወልዳበት ግራ እንደገባው
ያማክረኛል ። የቤተሰብ ምጣኔ ቢሮውን ጠቁሜው ተለየሁት ። ከአመታት በኋላ ስታዲየም
ሰልፍ ላይ ተገናኝተን ጠየኩት ። ሰውየው ፥ አመስግኖኝ አላቧራ አለ ። ሰልፉ ስላሰለቸኝ
ወሬ አሰፋሁ ...
እ...ግ...ዚ...ኦ !
ኢህአዲግ በገባ በሰማንያዎቹ መጨረሻም ኤሮቲክ አርት ተፋፍሞ ነበር ይባላል ። ጋዜጦች
ቢኪኒ ያረጉ አክትረሶችን በፊት ገፃቸው ያወጡ ነበር ። የነስብሃትና ሌሎች ላፓሪዚያን
አይመሽ የለን መሸና አገር ሰላም ብዬ እያፏጨሁ ስገባ ዘመድ አዝማድ አይኑ እኔ ላይ ነው
። እንዳየኋቸው ከአደነጋገጣቸው የሆነው ሁሉ ገባኝ ። የመጨረሻ ቃሌን አወጣሁ ።
KALKIDAN GENET
Ever since
God sins through Man carrying the ancestral sin
Fulfilling his interest without having to be a man himself
And the man goes to Sunday churches to confess his questions
Of being a first time human
“Forgive me father for I have sinned” he’d say
When in fact he did nothing but lived
ዲር ፒሰስ...
BEZ BROWN
ብታይ
(ማህተቤ)መስቀሌ ተሸረፈች
ቀሽ አለች..
ምፅ
(የመጨረሻው ቻው)
KALKIDAN TADDESSE
ከለውጥና ከእንቅስቃሴ የራቀ የገጠር መንደር ውስጥ ከትሜ እዚሁ ሳረጅ ፤ ውስጤ ግን
ከመንደሯ ራቅ ብለው ጎጆ የቀለሱ ፤ ማረፊያ ሲያሻቸው ብቅ የሚሉ ከተሜዎችን ሀገርና
ኑሮ ብቅ ሲሉ በጣሉላት አሮጌ መፅሀፍት ውስጥ ተዟዙራ እየታዘበች የምትደመም ተጓዥ
እኔ ተቀምጣለች።
Photo:Kirub El
እትም-14 ነሐሴ| 2012
17
ELROI ASHURO
በቅድሚያ ይሄ ሀሳብ ከብዙ ማሰላሰል እና ከ70 በመቶ መሰላቸት በኋላ የተገኘ መሆኑን
ማስገንዘብ እፈልጋለሁ (ማስ እና ገንዘብ … ማስ = mass፣ massገንዘቡ = ክብደት
ያለው ገንዘብ ..ምን እያልኩ ነው ዋጋ አለው!)
የዛሬን አያድርገውና በጥንቷ ህንድ የንጉስ ልጅ የዙፋን ተረካቢ የሆነው፣ ልኡል የነበረው
ሲዳርታ ጉተማ ቡድሀ (ስሙ ግን የሶስት ጓደኛሞች አክስዮን ማህበር ይመስላል ሲዳርታ፣
ጉተማ እና ቡድሀ (ሲጉቡ) ሲጉቡ የኑግ ዘይት አከፋፋይ ፕሪቪትድ ሊሚትድ)
አባቱ ከአለም ሰውሮ፣ ከስቃይ ከልሎ… ከመከራ ከድብርት እና ከርሀብ ሸፍኖ …ድሎት እና
ምላስ ሰንበር ብቻ እንዲበላ አድርጎ ያሳደገው ድልቡ ብድሀ (ይመስለኛል ካልሆነማ ታሪኩ
ሲቀጥል የተራበ ሰው አይቶ ..ወደ ውስጥ የገባ ሆዱን በንግስና ዱላው ጠቅ ጠቅ እያደረገ
እየነካካ ‹ሰውየው ካለ አንጀት ነው እንዴ የተፈጠርከው!› ባላለ ነበር) ታስቦና ተወስኖ
ድሎቱን ብቻ እንዲያይ ተደርጎ ነው ያደገው ለማለት ነው
እና በሱ መነጽር በwid እንደጦዘ ራስታ.. በደስታ ቀለማት ብቻ የምትታየው አለም አንድ
ቀን መስታወቷ እረገፈ …ስገምት 18 አመቱ አካባቢ ይሆናል እናም የአገጭ የደረት እና
የብብት ጸጉሩ የበዛለት ሰሞን.. ለንግስናው የምትሆን ቆንጆ ኮረዲት (ቄሮይት) ማየት
ሲገባው የበላው ምሰሳ እንዲፈጭለት ወክ እያደረጋ ሳለ የቤተመንግስቱን አጥር ተደግፈው
ያሉ ጠኔያም ህንዳውያንን ከነስቃያቸው ለመጀመሪያ ግዜ አያቸው(እንተኛው ታሪክ
እህል ሊሰርቅ የገባ ረሀብተና ተይዞ አይ ነው ግን ለኔ ታሪክ ስለማይመች ቀይሬዋለሁ)
እናም የፈጠጡ አትንቶችን ፣ የተጋጡ የተራቆጡ ሰውነቶችን ሲያይ ቡድሀ ክፉኛ ደነገጠ
ከመደንገጡ የተነሳ የበላው ምሳ ተፈጨ.. ደንግጦ አላበቃም እየሮጠ ወደ ክፍሉ ሄደ
(የሚያሳዝነው አጥሩ ጠባቂ ነው ቡድሀ የራበው ሰው እንዳይ የተሰጠውን ሀላፊነት
ባለመፈጸሙ ከደሞዙ ተቆርጦበታል ያውም ከአንገቱ ጋር)
ቡድሀ አለም ተገላበጠበት… ስቃይና ደስታን መመዘን ተሳነው… በኋላ ሲጣራ ድህነትን
ነው ከነአንጀቱ ያየው.. ከሱ ውጭ ያሉት ሁሉም ህንዶች ግን.. ከቆዳቸው አልፎ ድህነትን
በዲኤንኤ በዘረመል እና በዘር ፍሬያቸው ጭምር ተነቅሰውታል
ለማሳጠር ቡድሀ የአባቱ ውሸት እና ድሎት ነዶት ወደ ጫካ ሄደ (የራሱ ሳይሆን
የሰው ብሶት የወለደው ቡድሀ መሳሪያ ሳይዝ ባዶ እጁን ወደ ደደቢት ጫካ ወረደ በሉ
ከፈለጋችሁ.. ደደቢት ግንጫካ ነው)
የሆነ ሆኖ ቡድሀ ድህነትን ለመረዳት እያሰላሰለ እረጅም አመት በጫካው እድሜ
ሲራመድ ከቆየ በኋላ ደከመው ደከመውና ዝሎ ወደቀ ከወደቀበት ሲነቃ የማርያም ልደታ
ከሚከበርበት ቅቤና ቡና ከጠገበ ዋርካ ስር እራሱን አገኘው (ያቺ ዋርካ ቀጥላ በኢትዮጵያ
ታሪክ የኦነግ ባንዲራን ወለደች)
እንግዲህ ቡድሀ ያንን ሁሉ አመት ስለህይወት ትርጉም ሲያሰላስል በርሀብ ያልሞተው
የዋርካውን ቅቤና ቡና እየጠጣ ነበር ለካ .. ይሄ ሌባ! (ከሁሉም ተአምረኛ ቅዱሳን ጀርባ
አንድ የቅቤ ዋርካ እና የልደታ ጽዋ ማህበሮች አሉ የሚሉት ለካ ውሸት አይደለም) …
ወዴት እየሄድን ነው? … አዎ ወደ ኒርቫና … ቀጥሎ ወደ ማህበርተኞቹ ቆይ ደርሰናል
ቡድሀ ከእንቅልፉ ነቃ … አይኑን ገለጠ የጽዋ ማህበርተኞቹ ከዛፋችን ስር ዞር በል አይነት
እትም-14 ነሐሴ| 2012
20
አፍጥጠውበት አየ ‹ኒርቫና› ብሎ ጮኸ …ግራ ተጋብተው አዩት ያስተምራቸው ጀመር
ስለኒርቫና ኒርቫና ሁሉን የተረዳ ሁሉን ያወቀ ሁሉንም የማይሻ መሆን ነው.. መፈለግ
እና ማጣት የሌለበት ህልውና ነው … በዚህች አለም የስቃያችን ምንጭ መፈለጋችን ነው
አላቸው … እነሱ ትእግስት አተው ይመለከቱታል …ከዚህች አለም ስቃይ የምንድነው
ኒርቫናን ስንይዝ ከሁሉም ጋር እንድ ስንሆን ነው የማህበሩ አባላት ‹እኛ በአማላጇ
አንዴ ድነናል… ‹አሁን አንተም ይቺ ኒርቫና የምትላትም ሁለታችሁንም ነርቫችሁን
ሳናጠፋው ከዋርካችን ተነስ› ተጋፈጡት …እነዚህ ድሆች ከነድሪቶዋቸው ከነተጣበቀ
አንጀታቸው በደንብ አጤናቸው .. ቡድሀ ወደራሱ ተመለከተ ቡና እና ቅቤ ያጥወለወለውን
ሆዱን አሻሸ .. የሰውነቱ ቆዳ አጥንቱ ላይ ታጥቦ እንደተሰጣ አንሶላ በንፋስ ይወዛወዛል
… ‹ተነስ እንጂ› ድሆቹ ያላቸው አልራሩለትም … ድህነቱን ጠላውም፣ በቤተመንግስት
ህይወቱ የልጅነት ደስታው በአይኑ ውልብ አለበት ለካ ሁሉም ነገር ነበረው …ችጋር የያዘው
ሰው አይቶ ለምን ህይወቱን እንደጣለ! ለምን የሱ ጥፋት እንደመሰለው ተቆጨ… ከነዚህ
ድሆች ያውም ድሀ መሆናቸውን ከማያውቁ ሊሰውረው የሞከረውን አባቱ ትክክል
እንደነበር ተረዳ… ሲዳርታ ጉተማ ቡድሀ…እጁ ላይ የቀረችውን አንድ ጥሬ ቡና በትግል ወደ
አፉ አስገብቶ ሳይቆረጥም ዋጣት… ኮብል እስቶን የዋጠ መሰለው ጉሮሮው ላይ ተሰንቅራ
ቀረች… እንደምንም ድምጽ አወጣ… ‹የስቃያችን ምንጭ መፈለጋችን ነው› የሚለው
ላይ አንድ አረፍተ ነገር ጨመረ…‹የራሳችን ሳያንሰን የሌላው ስቃይ ምን አገባን› አለ እና
እስከወዲያኛው አሸለበ … ወደ ኒርቫና አለም፣ ምንም ምኞት ምንም ፍላጎት ወደ ሌለበት፣
ማግኘት ማጣት ወደ ማይጨንቁበት አለም … ወደ ሞት … ከዋርካው ስር ተደፍቶ ቀረ
… የቸኮሉት ማህበርተኞች ከዋርካው ጋር የተጣበቀ እግሩን ለስንት ታግለው ከነስሩ ነቀሉት
..ልክ ሲነቅሉት ቡድሀ አካሉ ወደ ደረቀ ዛፍነት ተቀየረ እነሱም ወድያው ወደ ፍልጥነት ወደ
ማገዶነት ቀየሩት …ቄጤማ ጎዝጉዘው ጀበናቸውን ጥለውበት ቡናቸውን ማፍላት ጀመሩ
…እየተሳሳቁ እየተመራረቁ… ቡናው ሲፈላ <ኦኦኦምምምምምም!> የሚል ድምጽ ወጣ።
ይፍቱሥራ ምትኩ
ስንኖር ስንኖር...
እኔ አህያዋ...
ምነዋ ውዴ?’ አልኩ... ምነው ጅቦ አይደለም.... ምነው ውዴ? አልኩ::
ሳሬን እግጣለሁ:: ሞልቶ የሚፈስሰው ሃብታም ነው:: ብዙ ገባር አህዮች
አሉት...’ማውቃቸውም ‘ማላውቃቸውም::
እሱ ጅቤ.... ‘እኒያን አህዮች እዪ ማደርጋቸውን’ ሲል እሰማ ነበር:: ውዴ ጅቤ
ይህንን ሲል ‘አህያዬ ሆይ...’ እያለኝ ነው ብዬ እንዴት ማሰብ እችል ነበር? ሌሎችን
ሲረግጥ...ሲጭንባቸው ‘...ለኔ ብለህ ስማ’ ሚለውን ተረት እንዴት ረሳሁ? ለካ ተረት
አልወድም...አላውቀውም ነበር ቀድሞውንም::
ስንኖር ስንኖር....
‘አህያና ጅብ ሲኖሩ ሲኖሩ....
ሌላ ቀን...
ጅብ ለአደን ወጣ... እንደወትሮው ወዲያ ወዲህ ቢልም አልቀናውም ያን’ለት::
ጅብ ጅብ ሆኖ መጣ ተርቦ::
አንክቶ
አንክቶ
ጋብ ሲልለት ራ’ቡ
‘አደራ’ አለ ለአያ ውሾ..
አደራ የልቧን ነገር....
ውሻ ይስቅ ይመስለኛል
ከጉበት ኩላሊት ፊት ልብ ልቤን አጣጥሟል...
ቀረጣጥፎ አጣጥሞ ጠግቧል
ያስባል ኇላ የሚገጥመውን
የሚጠየቀውን
‘ምነው አያ ውሻ ልቧስ?’
ይመልሳል...
ልብ ቢኖራት ቀድሞውን ካንተ ትወዳጅ ኖሯል?
ያብራራል
ያብራራል...
አለቅሳለሁ እኔ...
ወይ ልቤን ልቤን ኩላሊቴን....
Stop screaming! You little cunት you don’t even remember who I am,
do you? You are so far up your ass that you don’t even remember me!
How long has it been? Try, it has been too long since you used your
brain, but try.
I don’t know.
Hahahaha.... you don’t even know what you are going to do. You don’t
even know me. I can’t let you live cunት። This is your last day. You
screamed already shut the fuck up. Life is a game cunት and you have
wasted your lifeline. Noone can hear you dear God. What day is it? Ding
ding ding its Saturday and noone is at home. I chose this day. You still
haven’t figured it out have you, I am you. I am Jigsaw. Shake that dumb
face of yours all day, it ain’t gonna change shit. I finally am here to end
this nonsense. I let you see what I want you to see. I am a salesman re-
member የበአል ታላቅ ቅናሽ ተብሎ ስለተለጠፈ ብቻ ዘው አትበል። Look at your
hands you must like the blood. You were too much of a chicken to do
it. I am here no worries. You see the trick to cutting your wrist is to have
a sharp knife. Even if you have second thoughts it would be too late.
This is your last day cunት, that’s why I chose Amy Winehouse for you.
“Das Ende” cunት። You should have gone when you had the chance like
Heidi Turner.
ዘ ሚስካልኩሌሽንስ
AD MINO
አ᎐
“አሮጌዎቹ ዘፈኖችና የሽማግሌዎቹ ተምኔቶች” ሁሌም የሚያጨናንቋት ነገሮች
ናቸው። “ያለፈው” ብላ በነሲብ የምትፈርጀው ጊዜ እና ከሱ እንደምንም ተርፈው
“አሁኗ”ን የሚጋሯት ሰዎች አይመቿትም። ይኸንንም በግልፅ ቋንቋ ለጓደኞቿ
ትናገራለች።
ያየኋት ጊዜ ታክሲ ውስጥ ነበረች። ሰንበት ማለዳ ስለነበር ከባለንጀራዎቿ ጋር ወደ
አምልኮ ቦታ እየሄደች ነበር። ባለንጀራዎቿ ያልኳቸው፣ ዕድሜዎቻቸው አስራዎቹን
ወደ መጨረስ የሚያደሉ አንድ ወንድና ሁለት ሴት ታዳጊዎች ናቸው። በግራ
እጆቻቸው ጥቁር ሽፋን ያላቸውን ሐዲስ ኪዳኖች ይዘው፣ ስለ ሴት ፓስተሮችና ስለ
አክሮባቲስት ጓደኛቸው እያወሩ ነበር።
ወንዱ ጓደኛቸው ብዙ ባያወራም ማሰሪያውን አረፍተነገር ጣል እያደረገ፣ ብዙውን
ጊዜ እየተዋጠ ያወካሉ። የልጁ ነገር ለምን ትኩረቴን በጣም እንደሳበው ባይገባኝም፣
በተለይ ስለ ሴት ፓስተሮች ያወሩትን መርሳት አልቻልኩም።
“ሴቶቹ ፓስተሮች ነብይ ነው ሚባሉት!”
“ሴት ፓስተሮች ያስጠሉኛል። በተለይ ያረጁት!” አለችው። ወሬው የሰለቻት መሰለኝ።
ታክሲው ውስጥ ያለው ሙዚቃ የእጅጋየሁ ሽባባው ዘፈን ነው። ካህኔ ነፍሴ አገልጋዬ
᎐ ᎐ ᎐ ትላለች።
-
ቡ᎐
ከምንማርበት ግዙፍ ሆስፒታል ማዶ ያለው የከተማው ክፍል ገጠር ቀመስ እና
ዘፈቀደ አሰፋፈር ያለበት የተራራ ደረት ነው። እዚህ ፎቁ ላይ ሆኖ አረንጓዴውን ጋራና
የገበሬዎቹን ቤቶች ማየት ቀላል ነው። ከተማው ከዚህ ከሐኪም ቤቱ ፊት ለፊት
ካለው አስፋልት ጀምሮ እየሳሳ እየሳሳ ይሄድና የዳገቱ ሥር ሲደርስ ጥቂት የጨረቃ
ቤቶች ብቻ ያሉበት የእርሻ ስፍራ ይሆናል። ቤቶች፣ ቤቶች፣ የኮካኮላ ሎጎ የተሳለበት
የቆርቆሮ አጥር፣ ቤቶች፣ የዛገ ቆርቆሮ፣ የዛገ ቆርቆሮ፣ አዲስ ቆርቆሮ ᎐ ᎐ ᎐ በቆርቆሮ
የተሰራ ማስጂድ። የቆርቆሮ ሚናራ ያለው። ሌላ የጭቃ ቤት፣ ሌላ የጭቃ ቤት ᎐ ᎐ ᎐
ሌላ የቆርቆሮ ማስጂድ። የቆርቆሮ ሚናራ ᎐ ᎐ ᎐
-
ጊ᎐
ሲ᎐ እና እኔ ብዙ ጊዜ ተከራክረንባቸው ካልተስማማንባቸው ነገሮች አንዱ፣
“ሐይማኖት የዚህች ሐገር ብቸኛው የሞራሊቲ ጠባቂ ተቋም ነው እና አይደለም።”
ነበር። እሱ እንደሚለው፣ የሶስተኛው ዓለም ሐገራት እንዳይበለፅጉ ማነቆ ሆኖ
ያሰራቸው ዋነኛው ነገር የሐይማኖት ገናንነት እና አድሐሪ አዝማሚያ ነው። በርግጥ
ሲ᎐ ማለት የለየለት ኢአማኒ ነው። እግዜርን የካደ ብዬ ብገልፀው በውስጠታዋቂነት፣
እትም-14 ነሐሴ| 2012
27
“እግዜር አለ፣ ሲ᎐ ግን መኖሩን አያምንም።” ማለት ይሆንብኛል። ብቻ ግን ኢአማኒ
ነው።
-
ዳ᎐
አንዳንድ ቀን ከሆስፒታሉ ሶስተኛ ፎቅ ሆኜ ኃይለኛ የተሲያት ንዳድ የሚወርድበትን
የጋራውን ደረት እያየሁ እመሰጣለሁ። ሐኪም ቤት ከማንኛውም ምድር ላይ ካለ ቦታ
በላይ ሰቆቃ የሞላበት ሥፍራ ነው። የሆስፒታል ግድግዳዎች ከየትኛውም ቤተእምነት
በላይ ተስፋ የቆረጡ ፀሎቶችን ሰምተዋል የሚል ጥቅስ ሳላነብ አልቀረሁም። እነዚያ
ማዶ ላይ ጋራውን የሚቆፍሩ መሐይማን ገበሬዎች በየቀኑ ሶስቴ እና አራቴ እዚያ
የቆርቆሮ መስጂድ ውስጥ የፈጠራቸውን ያመሰግናሉ። ምክንያታቸው ደህንነታቸው
ወይም ሶስተኛ ልጃቸው ማግባቱ እና ወግ ደርሷቸው አያቶች መሆናቸው ይሆናል።
በዚያው ቅፅበት ጃፓን ውስጥ ሰዎች ህዋሳት ውስጥ ያሉ ሞለኪዩሎችን በዓይን
ማየት የሚያስችል ማሽን እየመረቁ ነው። ወዲህ ነጩ ግዙፍ ቤት ውስጥ የሆነ ሰው
በፅኑ ደዌ ይማቅቃል። የሆነ ነገር ትክክል ባይሆንም፣ ህማሙን ፈፅሞ ማስቀረት ግን
አንችልም።
-
ሄ᎐
ይቺ ልጅ ሽማግሌዎችንና አሮጊቶችን ብትጠላም እናቷንና አባቷን ግን ትወዳለች።
ቢያንስ እንደዛ ትላቸዋለች። “እማ ስወድሽ እኮ!”
የቤተሰቧ የበኩር ልጅ ናት። ብዙ የምታክመው ነገር ቤቷ እና ሰፈሯ እና አይኗካዋ
እና ከተማዋ ዙሪያ አለ። ዘወትር እንዳረፈደች ይሰማታል። ዘወትር ከጓደኞቿ እና
ከእኩዮቿ ኋላ ናት። (እስከዛሬ አልተሳመችም ሁላ እኮ!) እና የጊዜ ባዝራ ቀድሟት
እየሸመጠጠ እንደሆነ ታስባለች። ጊዜ ለአንዲት ልጃገረድ ምንድነው? ᎐ ᎐ ᎐ ባዝራስ? .
. . አሮጌው የመንዝ እና የደምበጫ ወይ የደምቢያ ሰዎች ቋንቋ?
-
ዉ᎐
ምናልባት የተራራው ልብ ውስጥ ዩራኒየም አለ። አለን ብዬ እንዳላወራ
የሚያደርገኝ “መጤነት” በዚህ አገር አድራጊፈጣሪዎች ግምባሬ ላይ ተለጥፎብኛል።
ልፋለመው አልፈልግም። ግን ገበሬዎቹ ምን እንደሚያርሱ እንኳን አያውቁም።
መሐይምነታቸውን ግን ብልጦች ይጠቀሙበታል። ብልጦቹ ፖሊቲከኞችና
ሐይማኖተኞች ናቸው። ቅድም ስለደሕንነታቸው ሲሰግዱ ቆይተው መስክ ላይ
ስለሚፀዳዱ በኮሌራ ይወድቃሉ። ፖለቲከኞቹ በሽታው ከሌላው ዓለም ስለጠፋና
ሰው ቢሰማው ስለሚስቅባቸው አዲስ ሥም ይሰጡታል። ሐይማኖተኞቹ ደሞ
የሚንቀጠቀጡ ጣቶቻቸውን ፀጉሯን ያልሸፈነችው የሰፈር ኮረዳ ላይ ይቀስራሉ።
ከቆሻሻ ጥፍሮቻቸው መንታ መንታ ፍላፃዎች ይወነጨፋሉ። ከሶስት ኪሎሜትር
ርቀት ዓይኖቹን አጥብቦ አወዳደቃቸውን የሚያየው ታዛቢ ጓደኛዬ ግን በነገሩ
ከንቱነት ደካማ ምፀቱን ይፈግጋል።
ይላልም፡
“ሁላችንም ወደ ሞት እያዘገምን ነው። ይኸ ይኸ ድንቁርና ግን ፍፃሜያችንን
እትም-14 ነሐሴ| 2012
28
ያፋጥነዋል።”
-
ዞ᎐
ስለሷ ሁለት ነገሮች አሉ። አንደኛው ደማም ቆንጆ መሆኗ ነው። ሁለተኛው ነገር ደሞ
የነገሮችን ድብቅ ጎን ማየት የማትፈልግ መሆኗ። ይህንን ቆንጆ ጫማዋን ትወዳለች።
ሲፀዳ የተረፈውን እጣቢ ግን ትሸሻለች። የማይደከምበት፣ የማይሰለችበት፣ እንዳባቷ
የማያንጎላጁበት፣ እንደናቷ የማያንኮራፉበት ዓለም ትሻለች።
ቸርች የደረሱ ጊዜ ወንዱ ልጅ ቀድሟቸው ከታክሲው ለመውረድ ሲያጎነብስ ሱሪው
ዝቅ ስላለ ለአፍታ የመቀመጫውን ስንጥቅ አየች። እና መንግስቷ ፈራረሰ። በሷ
እድሜ እና ጥንካሬ ያለ ሰው ላይ እንደዚያ ያለ እንከን ማየቷ የእስከዛሬው እምነቷ
አሸዋ ላይ የተገነባ ቤት እንደነበረ አረዳት። እንደተከዳች አሰበች።
(ለሷ እንከን ነው የቂጥ ስንጥቅ፣ የገላ ክሽፈት። የሰውልጅ አካል እንደ መላዕክት
ከሥጋዊ ጉድፎችና ፍላጎቶች ነፃ እንደሚሆን፣ በምን እንደሚሆን ባይገባትም፣ ነፃ
እንደሚሆን ታምን ነበር።)
–
ሁልጊዜም ሞትን የምትፈራ አድርጌ አሰብኳት። ግን አሁን ሳስበው ሳልሳሳት
አልቀረሁም። ሰው ሞትን የሚፈራው ስለ መረሳት አብዝቶ ከተጨነቀ ነው። የሷ
ጭንቀት ስለፍፅምና ነበር። ሞት ከፍተኛው የፍፅምና ክህደት ነው። እሷ እዚያ ረቂቅ
የሃሳብ ደረጃ ላይ ከመውጣቷ በፊት ቀለል ያለው የአካል ድክመት አሸነፋት። ያም
ሆኖ ከሲ᎐ ኢአማኒነት እና ከገበሬዎቹ አሳዛኝ ተረክ በተቃራኒው የምትቆም ናት።
(AUGUST, 2020)
****
የኛ ሙሽራ ዘመናይ
አበራች እንደጸሃይ....
****
****
እትም-14 ነሐሴ| 2012
32
እሷስ ሎሚ ናት ያባይ ዳር
ሎሚ ናት ያባይ ዳር
እኔስ መሸብኝ የት ልደር
ሎሚ ናት ያባይ ዳር....
አሻ ገዳዎ
በል አሻ ገዳዎ በል አሻ ገዳዎ
አሻ ገዳዎ
ዛሬ ምንድራት
ልጅት የኛ ናት......
________________
* ኒኬል
Time Travelers
Source: https://www.facebook.com/colorizinghistory
እትም-14 ነሐሴ| 2012
34
YIKUNOAMLAK M. GEBREHIWOT
I look to dawn,
... darkness begone.
I’m hopeful for brightness,
... instead I’m met with vagueness.
ሮዛ
WILILY BALD
ብግን ቅጥል እያልኩ ዛፉ ስር ሄጄ ተቀመጥኩ። አስጠሉኝ! እዩት ደሞ ናቲን
ይሄ ብሽቅ! እላለው በሆዴ። “ስሙ ምንድነው የሚባለው?” አለች ሮዛ ከጎኔ
እየተቀመጠች። “ሀርሞኒካ ነው የሚባለው። ስሙን እራሱ አያውቁትም እኮ!
ሲያስጠሉ!” አልኩ በንቀት እያየኋቸው። ሮዛ ዝም አለች። ዛሬ ገና ነው ያወራነው።
እሷም ሆነ እናቷ ከሰው አይገጥሙም ለጨዋታ እንኳን ከስንት አንዴ ነው
የምትወጣው። ስትወጣም እዚህ ዛፍ ስር ቁጭ ብላ ሌሎቹ ሲጫወቱ ማየት ነው
ስራዋ። እየተጫወተ ያለ ልጅ ቤት ሲጠራ ወይም ለጨዋታ ሰው ሲያንስ ነው
የምትጠራው ያውም ሰብለ የቄሱ ልጅ እና ፍቅርተ ድፎ እሺ ካሉ። እናቷ ሴተኛ አዳሪ
ናት። አባቷ ከሞተ ቆየ ይላሉ። እናቴ ስትነግረኝ እሱ የሞተ ቀን እናቴ እኔን ወልዳ
ከሆስፒታል ቤት መግባቷ ነበር። ቀበር ካልሄድኩ ብላ አስቸግራ ቤት እንደተቆለፈባት
ነግራኛለች። የሮዛ እናት ቲቲ ነው የምትባለው ድሮ የእናቴ፣ የእትዬ አበዛሽ፣ እትዬ
ፅጌ፣ እና እትዬ ምስራቅ ጓደኛ ነበረች. . .አሁን ከእናቴ በቀር ማንም አያዋራትም። እኛ
ቤት ስለ ሮዛም ሆነ ስለ ቲቲ ምንም አንባልም። እነ ናቲ፣ሰብለ፣ፍቅርተ እና ሰላም ግን
ስድብ ሁሉ ተነግሯቸው ነው የሚመጡት። ሮዛ ከቤት ወጥታ ዛፉ ስር ቁጭ ስትል
የሚዘፍኑት የስድብ ዘፈን ሁላ አላቸው።
ትምህርታዊ ጉዞ ወደ ምድር
ቢንያም
ዛሬ በ ፕላኔት G-369 ላይ የሚገኘው svora highschool ጉዞ አዘጋጅተው የ
ዘጠነኛ ክፍል ተማሪዎቻቸውን በህዋ ላይ በማንሸራሸር የሚያስጎበኙበት ቀን
ነው። ተማሪዎቹም ጓጉተዋል። መሬት ላይ የሚኖሩ ሠው ስለሚባሉ ነገሮች ብዙ
ሰምተዋል። ብዙ ተረትም እየሰሙ አድገዋል ቀርበው ግን አይተው አያውቁም ነበር።
ስለዚህ የዛሬዋን ቀን በጉጉት ሲጠብቋት ነበር። ሁሉም በጠዋት ነበር ይዟቸው ወደ
ህዋ በሚበረው የህዋ መርከብ ጋር የተገናኙት። ጉብኝታቸውም በመምህር ጋንቮር
እና በመምህርት ሊቪያር የተዘጋጀ ስለነበር ሁሉም ተማሪዎች ወደ ህዋው መርከብ
መግባታቸውን ካረጋገጡ በኋላ በሩን ጥርቅም አድርገው ዘጉት።
“እሺ ተማሪዎች እንዴት አደራችሁ። ዛሬ እንግዲህ በህዋ ላይ ዞር ዞር እያልን ያሉትን
ፕላኔቶች እና እላያቸው ላይ የሚኖሩትን ፍጡራን እንጎበኛለን።” አላቸው መምህር
ጋንቮር
” መምህርት ሊቪያር የምትጨምሪው ነገር ይኖራል?”
” አዎ። ያው እንደሚታወቀው ጉዟችን ትንሽ ራቅ ስለሚል ሁሉንም ማየት አንችልም
ግን በእናንተ ምርጫ አንዱን ፕላኔት በደንብ እናያለን። ስለዚህ ተማሪዎች አሁን
ፕላኔት ምረጡ።”
ተማሪዎቹም በአንድ ድምፅ ‘መሬት’ አሉ።
መምህርት ሊቪያርም ፈገግ ብላ
” በጣም ጥሩ። ጉዞ ወደ መሬት። ሁላችሁም ቀበቷችሁን በደንብ እሰሩ። እኛ ተነሱ
እስከምንላችሁ ድረስ ቁጭ በሉ።እሺ። ጥሩ። እንሂድ በሉ።” አለችና ጉዟቸውን
ጀመሩ። ወደ መሬትም በተጠጉ ጊዜ የህዋ መርከቧን አቁመው መምህራኖቹ ገለፃ
ያደርጉ ጀመር
“እንግዲህ ተማሪዎች ይህ የምትመለከቱት ትልቅ ሰማያዊ የድንጋይ ኳስ
የሚመስለው ፕላኔት መሬት ይባላል። ከፀሐይ በሶስተኛ ደረጃ ላይ የሚገኝ ፕላኔት
ሲሆን በውስጡም ሠው የተባሉ ትናንሽ ፍጡራን ይኖሩበታል። መልካቸውም ትንሽ
ያስፈራል። እንደኛ ቆንጆ የሚባሉ አይደለም። ኩራታቸው ግን ከቁመታቸው እና
ከእውቀታቸው በላይ ነው። በህይወታቸው የሚገርሙ ህጎችና የአኗኗር ዘዴ አላቸው
። ድሮ ድሮ በቁጥር ብዙም አልነበሩም። አሁን ግን በጣም በዝተዋል።የያዘቻቸው
ምድር ከበቂ በላይ ብትሆንም እነሱ ግን ተደራርበው ተጣበው መኖርን ይመርጣሉ።
ባለቻቸው ትንሽ የእውቀት ብናኝም ይኩራራሉ። ከሙሉ ህዋው ውስጥ ህይወት
ያለን እኛ ብቻ ነን ብለውም ያስባሉ።”
” ለምንድነው እንደዛ የሚያስቡት?” ጠየቀች አንዷ ተማሪ
” ትንሽ ወደ ህዋ ተጉዘው ጓሮ እና ዙሪያቸውን አየት አየት አድርገው ሌላ እነሱን
የሚመስል ነገር ስላጡ በቃ እኛ ብቻ ነን ብለው ያስባሉ። ብዙም አልራቁም። ያን
ያህል የሚያስጉዝ እውቀት ላይ አልደረሱም። ባገኙትም ሌላ ፕላኔት ላይ ሁሉ ለነሱ
እትም-14 ነሐሴ| 2012
41
የሚስማማ መሆኑን እና አለመሆኑን ያጣራሉ።”
” ለምን? እዛም ሊኖሩ አስበው ነው?” ጠየቀ ሌላ ተማሪ
” አዎ። ያሉበት ፕላኔት እየሞተች ነው ብለው ስለሚያስቡ አብረን አንሞትም
በማለት ሌላ መኖሪያ እየፈለጉ ነው።” አለች መምህርት ሊቪያር
” ፕላኔታቸው ለምንድነው የምትሞተው?” የማያልቀው የተማሪ ጥያቄ ይዘንባል
” ራሳቸው በአግባቡ ስላልያዟት ነው። የሚገሏት ራሳቸው ናቸው። በምድር ላይ
የሚገኙት የሚያስቡ ፍጡራን እነሱ ብቻ ቢሆኑም እርስ በርስ ግን አይስማሙም።
በዚህች ትንሽ ፕላኔታቸው ውስጥ ብዙ መከፋፈሎችን ለራሳቸው አዘጋጅተዋል።
በምናባቸው የፈጠሩት ድንበር የሚባል ሐሳባዊ መስመር ስላላቸው በሐገር
ይከፋፈላሉ። በቋንቋ ፣ በሰፈር ፣ ባላቸው ብር መጠን ፣ በፆታ ፣ በሀይማኖት ፣
በሁሉም ነገር እርስ በርስ ተከፋፍለው የሚጣሉበትን ሜዳ በራሳቸው አስፍተዋል።
ሌላው ቀርቶ በቆዳቸው ቀለም ይከፋፈላሉ።”
ተማሪዎቹም ሳቃቸውን ለቀቁት “ማለት?” አለ አንዱ ተማሪ
“ማለትማ የአንዱ ቀለም ነጭ ከሆነ የአንዱ ደግሞ ጥቁር ከሆነ በቃ ይከፋፈላሉ –
ጠላት ይሆናሉ። ” አላቸው መምህር ጋንቮር አብሯቸው እየሳቀ
“ከነሱም ብሶ ደግሞ በቀለማቸው ይጣላሉ ለራሳቸው እኮ ምን እንደሚመስሉ
አላወቁ” ብላ መምህርት ሊቪያርም ሳቀች
“እኛ ለምን ቀርበን አናናግራቸውም ግን?” አለ ፊት ለፊት የተቀመጠው ተማሪ
” ለጎረቤቶቻቸው ያልተመለሱ ከሌላ ፕላኔት የመጣውን እንዴት አድርገው
ይምሩታል። ገና ለመናገር አፋችንን ሳንከፍት ነው ግራ ቀኝ ብለው የሚገሉን። ዝግጁ
አይደሉም። መጀመሪያ የራሳቸውን ችግሮች ከፈቱ በኋላ እኛም ቀርበን ለማናገር
እንሞክራለን። እስከዛ ግን በሩቁ ነው የሚያዋጣን። እንደዚህ ስላችሁ ግን ጥላቻ
ብቻ የተሞሉ ናቸው ማለቴ አይደለም። ስለሚፈሩ ነው። ከነሱ የተለየ ነገር ይፈራሉ።
ግን ጥሩ ነገር ይፈልጋሉ። የሚያደርጉት ነገር ሁሉ ጥሩ ነገርን ፍለጋ ነው። የተሻለ
ለማግኘት ብለው ሲሮጡ ነው ብዙ ነገር የሚደፉት። በቴክኖሎጂ ቢያድጉም ግን
ቴክኖሎጂ ላይ ቀርተዋል። ነገሮችን በመስራት ተራቀዋል። ራሳቸው ላይ መስራት
ላይ ግን ወደ ኋላ ቀርተዋል። እንደውም ከነሱ እንሻላለን ብለው ከሚያስቡት
ከመጀመሪያዎቹ ሰዎች ይልቅ የአሁኖቹ ከቴክኖሎጂው ውጪ ወደ ኋላ የቀሩ
ናቸው። ወደ ውጪ መስራት ላይ ጎበዝ ናቸው። ወደ ውስጥ መስራት ላይ ግን ብዙ
ይቀራቸዋል።” አለ መምህር ጋንቮር
” እሺ ለመዋለድ እንዴት ነው የሚጠራሩት? ማለት ወንዱ ወይም ሴቷ ምን አይነት
ድምፅ ነው የሚያወጡት?” ብሎ አንድ ተማሪ ጠየቀ። ሌሎቹ በእፍረት ሳቁ።
” አይ እንደሱ አይደለም ተማሪዎች። በእርግጥ ለመዋለድ ሲፈልጉ ድምፅ ባያወጡም
የራሳቸው የሆነ መንገድ አላቸው። በፊት በፊት ፈላጊው ወደፈለገው ሰው ይሄድና
ራሱን ያስተዋውቅና የሚፈልገውን ሳይናገር ግን በጊዜ ሂደት እየገለጠ ሲሄድ
ተፈላጊውም ከፈለገ ያው ይስማማሉ ማለት ነው። አሁን ያሉት ደግሞ ከየትኛውም
ትውልድ በበለጠ ከቴክኖሎጂ ጋር ጥብቅ ቁርኝት ስላላቸው ሁሉን ነገር የሚያደርጉት
እጃቸው ላይ ባለች ሞባይል ብለው በሚጠሯት የቴክኖሎጂ ውጤት ነው። በሞባይሉ
ተጠቅመው ወይ በፊደላት ይፃፃፋሉ ወይ ደግሞ በድምፃቸው የፈለጉትን
እትም-14 ነሐሴ| 2012
42
ያስተላልፋሉ ማለት ነው። ግን ደግሞ ኩራት ስላለባቸው የነሱ የመጠራራት
ጨዋታ የሚያመዝነው ማን የበለጠ ያልፈለገ መስሏል ላይ ነው። ግራ ያጋባል
አይደል? እንዴት መሰላችሁ አሁን አንድ የሰው ፍጡር ሌላን የሰው ፍጡር ሲፈልግ
በተቻለው መጠን ያልፈለገ ለመምሰል ነው የሚጥረው።”
“እንዴ እየፈለገ ለምንድነው ያልፈለገ የሚመስለው? ተቃራኒውን?” አሉ ተማሪዎቹ
” አንዳንዴ ግራ የሚገቡ ፍጡራን ናቸው። ያላቸው ኩራት ዘላለም የሚኖሩ ያህል
ነው። ሁሉን ነገር ሳያዩ በፊት የሚያልፉ አይመስላቸውም። አጠገባቸው እንኳን
ሌላው ሲሞት እያዩ በዛው ኩራታቸው ይቀጥላሉ። ጊዜ አለን ብለው ያስባሉ።
ስለዚህ ለመኖር ጊዜን ይጠብቃሉ። ግን ለመኖር መጠበቅ ማለት ለመሞት መጠበቅ
ማለትም እንደሆነ አያስተውሉትም። የገዛ አእምሯቸው ያታልላቸዋል። የገዛ
አእምሯቸው ገዝቷቸዋል። አብዛኛዎቹ ራሳቸውን ይህ የድንጋይ ኳስ ላይ ስላገኙት
ብቻ ነው የሚኖሩት እንጂ ለምን ብለውም መጠየቅ አይፈልጉም። ለምን ቢሉም
መልስ የለውም። ግን መጠየቅ አለባቸው። ራሳቸው ጠይቀው ራሳቸው መመለስ
መቻል እንደሚችሉም ያስተዋሉት አይስልም። አሉ ደግሞ ከመሀላቸው የነቁ የበቁ።
ግን እነሱ ተሸፍነዋል። ብዙ ትናንሽ ነገር የሸፈናቸው ብዙ ታላላቆችም አሏቸው። ግን
አይሰሟቸውም። የሚሰሙት የጮኸውን ነው። የሚያስተጋቡትም የጮኸውን ነው።
በአሁን ሰዓት የሚጮኸው ደግሞ ከሰውኛ አፈጣጠራቸው ውስጥ መበላሸታቸውን
ወይም መንገድ መሳታቸውን በግልፅ የሚያሳየውን ነው። ለነገሩ እኛም ከውጪ
ስለምናያቸው እንጂ ግራ ተጋብተዋል እነሱም። ምንም ነገር ከውጪ ሲታይ ይቀላል
ልጆች። እነሱም ልክ እንዳልሆኑ ሲያውቁ ጊዜው ይረፍዳል። ልክ ሊሞቱ ሲሉ መኖር
እንዳልጀመሩ ይገለጥላቸዋል ያኔ ያልፋሉ። ህይወት ግራ መጋባት ነው – ሞት ሁሉን
ያጠራል።”
“መምህር እሱ ምን ማለት ነው? ሞት እንዴት ነው ህይወት የሚያጠራው?” አለች
አንዷ ግራ የተጋባች ተማሪ። መምህር ሊቪያርም ብትሆን መልሱን ማወቅ ፈልጋ
ስለነበር ትኩረቷን ወደ መምህር ጋንቮር አዞረች።
” ሞት ህይወትን የሚያጠራበት መንገድ እንዴት መሰላችሁ። አሁን ለምሳሌ
ከአምስት ደቂቃ በኋላ ትሞታላችሁ ይባል። ምሳሌ ነው። ምን ሊያስጨንቃችሁ
ይችላል? የቤት ስራ? የለበሳችሁት ልብስ ንፁህ አለመሆኑ? ሰው ስለ እናንተ
ምን እንደሚያስብ? ወይስ ስለ ወላጆቻችሁ? ስለ ወንድም እህቶቻችሁ?
ስለምትወዷቸው ሰዎች? ስለምን ታስባላችሁ? ሞት ሲመጣ ይዞት የሚመጣው
መጥረጊያ አለ። እሱ መጥረጊያ ደግሞ ህይወታችሁ ውስጥ ተሰግስገው ህይወትን
ከባድ የሚያስመስሏት ነገሮችን ጠራርጎ የማስወጣት ሐይል አለው። ስለዚህ ሞት
ህይወትን የማፅዳት አቅም አለው ማለት የማይረቡ እና እግሮቻችሁ ስር የተተበተቡ
ትናንሽ መሰናክሎችን አልፋችሁ ትኩረታችሁ እና ጊዜያችሁ መሆን ወዳለበት እና
ወደሚገባው እንድታዞሩ እድሉን ይሰጣችኋል። ሞት ነፃ ያወጣል። ለዛም ነው
ህይወት ግራ መጋባት ነው – ሞት ሁሉን ያጠራል ማለቴ። ግን ደግሞ ህይወታችሁን
ለማጥራት እስከ ሞት ድረስ መጠበቅ የለባችሁም። አመጣጡ አይታወቅምና
እድሉንም ላይሰጣችሁ ይችላል። ግን እንደሚሞት ሰው ስትኖሩ አኗኗራችሁ ወደ
እውነት የተጠጋ ይሆናል። የሰው ልጆችም ይሄ ቢገባቸው ኑሯቸው ይለወጣል።” ብሎ
እትም-14 ነሐሴ| 2012
43
መምህር ጋንቮር በረጅሙ ተነፈሰ
“እሺ ሌላ ጥያቄ። ያለው አለ?” አለች መምህርት ሊቪያር ሰዓቷን እያየች
” ቀርበን አናያቸውም?” አለች አንዷ ተማሪ
” እሱን እንኳን ማድረግ አንችልም። በአሁን ሰዓት ግራ የተጋቡበት ጊዜ ስለሆነ እኛም
ተጨማሪ ግርታን መፍጠር ስለማንፈልግ ከዚሁ ሆነን ቤታቸውን ብቻ እናያለን።
ስለነሱ አውርተን መጨረስ አንችልም ግን የቻልነውን ያህል ነካ ነካ ለማድረግ ነው
የሞከርነው። ምን እንደሚመስሉ ደግሞ በየመፅሐፍቶቻችሁ ላይ ምስላቸው እና
አፈጣጠራቸው ስለተቀመጠላችሁ እሱን ማንበብ ትችላላችሁ። ሰዓቱም እየሄደ
ስለሆነ እኛም መመለስ አለብን። ግን የመጨረሻ ልላችሁ የምፈልገው ነገር ምንድነው
እነዚህ ሰው የተባሉ ፍጡራን ተስማምተው አንድ የሆኑ ቀን – ወደ ውጪ ሳይሆን
ወደ ውስጣቸው የተመለከቱ ቀን በዚህ ማለቂያ በሌለው ህዋ ውስጥ ካሉት ፍጡራን
ሁሉ የበለጡ ሓያላን ይሆናሉ። በቴክኖሎጂ ብቻም ሳይሆን በ ሁሉም አቅጣጫ
ይበለፅጋሉ። ያኔ እውነተኛ ማንነታቸው ይገለጣል። ይቺን ቤታቸውን አቃጥለው
አመድ ሳያደርጓት በፊት እና እርስ በርስ ሳይተላለቁ በፊት ሁሉም አንድ እንደሆኑ
ቢገባቸውና መሆን እና መድረስ የሚችሉበትን ጥግ የሚያሳያቸውን ከነሱ መሐል
የሚገኙትን መከተል ቢችሉ ብዙ ነገር ላይመለስ ከመበላሸቱ በፊት ሊያድኑት
ይችላሉ።” አለች መምህርት ሊቪያር
“በሉ አሁን መመለሻ ሰዓታችን ደርሷል። ሌላ ጊዜ ሰፋ ያለ እና ምናልባትም ከሆነልን
እነሱ እንዳያዩን አድርገን ከመሐከላቸው ሆነን በቅርበት ስለ ሰው ልጆች እናጠናለን።
እሺ ተማሪዎች? በሉ አሁን ቀበቷችሁን እሰሩ” መምህር ጋንቮር ተኔገረና እሱም ቁጭ
ብሎ ቀበቶውን አሰረ። መንቀሳቀስ ሲጀምሩ ግን ተማሪዎቹ አዘኔታ ውስጥ ነበሩ።
“ሲያሳዝኑ ግን ” አለች አንዷ ተማሪ
ሁሉም ሐሳቧን ተጋሯት። ዞር ብለውም ወደ ምድር እያዩ ከንፈራቸውን መጠጡ።
ሲያሳዝኑ።